አካ ቦቹ፣ የ"ባሻገር" ጀግና። በሐሰት የግድያ ወንጀል ተከሶ፣ ነፍሰ ጡር ሚስቱን ትቶ ስምንት ዓመታት ሙሉ ተሰውሮ ኖሯል። ዛሬ ተመልሶ ንጹህነቱን ለማረጋገጥ እና የናፈቀውን ቤተሰቡን ለማግኘት እየታገለ ነው። ያኔ በሀሰት ያስወነጀሉት ጠላቶቹ አሁንም እሱን ከማሳደድ አላረፉም።
አካ ቦቹ ግን ሀቅን ሰንቆ አለመሸነፍን መርጧል! የእሱ ታሪክ የጠፋውን መልሶ ለማግኘት የሚደረግ የቁርጠኝነት ማሳያ ነው።